የታገቱ ሰዎች ጉዳይ ከምን ደረሰ ?

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ፦

➡️ ወደ ባቱ ሲጓዙ በታጣቂዎች ስለታገቱና እስካሁን ስላልተለቀቁ 3 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች ጉዳይ፤ (https://t.me/tikvahethiopia/86971?single)

➡️ ልጃቸው በሊቢያ ስለታገተባቸው የሀዋሳዋ እናት ፣  (https://t.me/tikvahethiopia/86852?single)

➡️ ልጃቸው በሊቢያ ስለታገተባቸው የአዲስ አበባው አባት ፤ (https://t.me/tikvahethiopia/86957?single)

➡️ ወደ ሳዑዲ አረቢያ ስትጓዝ የመን ላይ ታግታ 300 ሺህ ብር ስለተጠየቀባት ወጣት (https://t.me/tikvahethiopia/87107?single) መረጃዎችን ማድረሱ ይታወሳል።

ስለታጋቾች አሁንስ #ምን_አዲስ_ነገር_አለ ? በሚል ቤተሰቦቻቸውን ጠይቋል።

የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ታጋቾችን በተመለከተ አዲስ ነገር የጠየቅናቸው የአንዱ ታጋች እህት ወይዘሮ ራሄል ሶስቱም #እንዳልተለቀቁ ገልጸው ፤ “ ምንም አይነት ፍንጭ የሚሰጠንም አጣን። የት እንሂድ ? ምን እናድርግ ? ” ሲሉ በሀዘን ጠይቀዋል።

ልጃቸው በሊቢያ እንደታገተባቸው ገልጸው የነበሩት የሀዋሳዋ ወይዘሮ ገነት ጥላሁን ፥ “ አሁንማ ‘ ፓሊስ ከቧቸዋል ’ ተብሎ ስልክም ብንደውል አይነሳም። ስልካቸው ከጠፋ ከ15 ቀናት በላይ ሆኗል ” ሲሉ ገልጸዋል።

“ ትሪፓሊ ከተማ ከደረሱት ውስጥ መረጃ ስንጠይቅ ‘ፓሊስ መጥቶባቸው ነው ፤ ከበዋቸዋል አካባቢውን’ ” እንዳሏቸው ገልጸዋል።

“ ደላላውን 1 ጊዜ ብቻ አግኝቸው ‘ ፓሊስ ስለመጣብን ሌላ መጋዘን ወስደናቸዋል ’ አለኝ ” ሲሉ ተናግረዋል።

በተመሳሳይ ልጃቸው በሊቢያ ታግቶባቸው 700 ሺሕ ከከፈሉ በኋላ በድጋሚ 400 ሺሕ ብር ተጠይቀው የነበሩት የታጋች አባት አቶ አማረ አለም ፣ ለ2ኛ ጊዜ የተጠየቁትን ገንዘብ ካርታ አስይዘው ተበድረው ከላኩ በኋላ ልጃቸው #እንደተለቀቀ ባሕሩን ለመሻገር አስቦ ሞገድ ስለተነሳ ገና እየጠበቀ እንደሆነ ገልጸዋል።

ሳዑዲ ለመሄድ  ” ራጎ ” ላይ ስትደርስ በደላሎች 300 ሺሕ ብር የተጠየቀባት ታጋች ቤተሰቦች በበኩላቸው፣ ገንዘቡ ስላልተሟላ ገና እንዳልተላከ፣ ደላሎቹን ጊዜ እንዲሰጧቸው እየጠየቁ መሆናቸውን አስረድተዋል።

ውድ ቤተሰቦቻችን ፤ እገዛችሁን ጠይቀው የነበሩት ሁሉም የታጋቾች ቤተሰቦች ለረዷቸው ሁሉ ምስጋና አቅርበዋል።

በድህረ ገጻችን ኢትዮ አማዞን በመግባት የሚፈልጉትን እቃ ማዘዝ  ብቻ  ሳይሆን የርስዎንም እቃዎች መሸጥ እንደሚችሉ ስናሳውቅዎት በደስታ ነው ። ለማስታወቂያ ወይንም ለመግቢያ ምንም ክፍያ አይጠበቅብዎትም፤  ለተጨማሪ መረጃ   ድህረ ገጻችንን ይጎብኙ። https://ethio-amazon.com/

ለበለጠ መረጃ ሊንኩን በመንካት የቴሌግራም ግሩፓችንን ይቀላቀሉ!https://t.me/ethioamazon

ምንጭ (@tikvahethiopia )