ታግታ 150 ሺህ የአሜሪካ ዶላር የተጠየቀባት ህጻን ተገኘች።

የ2 ዓመት ከ8 ወር ዕድሜ ያላት አቢጊያ ዳንኤል የተባለች ህፃን ነዋሪነቷ በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ” ሳርቤት ‘ አካባቢ ሲሆን ከመኖሪያ ቤታቸው ተወስዳ ትታገታለች።

አጋቿ ቸርነት ጥላሁን የተባለው ግለሰብ ነው።

ግለሰቡ ከቤተሰቡ ጋር በነበረው ቅርበት ህፃን አቢጊያን በተለያዩ ቦታዎች እየወሰደ በማዝናናት እንደ ቤተሰቡ አባል ያጫውታት እንደነበረ እና ከ5 ወር በላይ ከቤተሰቡ ጋር  በትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪነት የነበረው ቅርብ ወንጀሉን በቀላሉ ለመፈፀም ምቹ ሁኔታን እንደፈጠረለት የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።

ግለሰቡ ሚያዚያ 25 ቀን 2016 ዓ/ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ተኩል ገደማ ወደ ህፃኗ ወላጆች መኖሪያ ቤት በመሄድና “እናቷ አምጣት ብላኛለች “ብሎ ለቤት ሰራተኛዋ ከነገረ በሗላ ህፃን አቢጊያ ዳንኤልን ወስዶ በማገት ገንዘብ እንዲሰጠው ከወላጆቿ ጋር ሲደራደር ቆይቷል።

ተጠርጣሪው ግለሰብ 150 ሺህ የአሜሪካ ዶላር እንዲሰጠው በመጠየቅ ገንዘቡን ማግኘት ካልቻለ ግን ህፃኗን በህይወት እንደማያገኟት ሲዝት ነበር።

የአዲስ አበባ ፖሊስ፤ ህፃኗን ለማስመለስ እና ግለሰቡን በቁጥጥር ስር ለማዋል ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር በመቀናጀት  ክትትል ሲያደርግ ቆይቷል።

በተደረገው ክትትልም ዛሬ ሚያዚያ 28/ 2016  ዓ/ም በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 አለም ሰላም ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ተጠርጣሪው ተከራይቶ በሚኖርበት መኖሪያ ቤት ውስጥ ለ3 ቀናት ያህል ታግታ የቆየችው ህፃን አቢጊያ ዳንኤል ልትገኝ መቻሏን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

ምንም እንኳን ፖሊስ ህጿን መገኘቷን ቢገልጽም አጋቹ በቁጥጥር ስር ስለመዋሉ ያብራራው ነገር የለም።

በድህረ ገጻችን ኢትዮ አማዞን በመግባት የሚፈልጉትን እቃ ማዘዝ  ብቻ  ሳይሆን የርስዎንም እቃዎች መሸጥ እንደሚችሉ ስናሳውቅዎት በደስታ ነው ። ለማስታወቂያ ወይንም ለመግቢያ ምንም ክፍያ አይጠበቅብዎትም፤  ለተጨማሪ መረጃ   ድህረ ገጻችንን ይጎብኙ። https://ethio-amazon.com/

ለበለጠ መረጃ ሊንኩን በመንካት የቴሌግራም ግሩፓችንን ይቀላቀሉ!https://t.me/ethioamazon

ምንጭ ( @tikvahethiopia )

 

 

Show Buttons
Hide Buttons