ሳፋሪኮም ፥ በ1.5 ቢሊዮን ዶላር 5,000 የቴሌኮም ማማዎችን ሊገነባ መሆኑን ገለጸ።

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ማማዎቹን የሚገነባው የኔትወርክ መሰረተ ልማትን በአገሪቱ የተለያዩ ቦታዎች ለማስፋፋት መሆኑን አስታውቋል።

በዚህም በቀጣዮቹ 3 ዓመታት የኔትወርክ ማማዎችን ለመገንባት ማቀዱን የገለጸው ተቋሙ ፣ ለግንባታው 1,5 ቢሊዮን ዶላን ፈሰስ ለማድረግ እንደመደበ ገልጿል።

የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዊም ቫንሄለፑት ባደረጉት  ገለጻ፣ “ ኔትወርካችንን ለማስፋፋት እና ለመላው ኢትዮጵያዊያን የቴሌኮም ትስስርን ለማሻሻል ከፍተኛ ጥረት እያደረግን እንገኛለን ” ብለዋል።

በአጠቃላይ የኔትወርክ ማማዎችን ቁጥር ወደ 7,000 ለማድረስ እየሰሩ እንደሚገኙ አስረድተው፣ “ በአሁኑ ጊዜ አገልግሎት ከምንሰጥባቸው 2,500 የቴሌኮም ማማዎች ውስጥ 1,5000 እራሳችን የገነባናቸው ናቸው ” ሲሉ ተናግረዋል።

በድህረ ገጻችን ኢትዮ አማዞን በመግባት የሚፈልጉትን እቃ ማዘዝ  ብቻ  ሳይሆን የርስዎንም እቃዎች መሸጥ እንደሚችሉ ስናሳውቅዎት በደስታ ነው ። ለማስታወቂያ ወይንም ለመግቢያ ምንም ክፍያ አይጠበቅብዎትም፤  ለተጨማሪ መረጃ   ድህረ ገጻችንን ይጎብኙ። https://ethio-amazon.com/

ለበለጠ መረጃ ሊንኩን በመንካት የቴሌግራም ግሩፓችንን ይቀላቀሉ!https://t.me/ethioamazon

ምንጭ (@tikvahethiopia )