የትግራይ ክልል ክለቦች ወደ ዋናው ሊግ ሊመለሱ ነው።

የትግራይ ክልል የእግር ኳስ ክለቦች ከጦርነቱ በፊት ወደ ነበሩበት ዋናው ሊግ ከቀጣይ 2017 ዓ/ም የውድድር ዘመን ጀምሮ ተመልሰው እንዲወዳደሩ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ወስኗል።

ፌዴሬሽኑ ከዚህ ቀደም አስተላልፎት የነበረውን ውሳኔ ሙሉ ለሙሉ በመሻር የትግራይ ክለቦች ከጦርነቱ በፊት ሲወዳደሩበት ወደነበረው ሊግ ተመልሰው እንዲወዳደሩ ከመንግሥት የቀረበውን አቅጣጫ በመቀበል ውሳኔ አሳልፏል።

በ2017 ዓ/ም የውድድር ዘመን 19 ቡድኖች ተሳታፊ እንደሚሆኑና 5 ቡድኖች ወደ ከፍተኛ ሊግ እንደሚወርጉ ተገልጿል።

በ2018 ዓ/ም የውድድር ዘመን ሊጉ ከዚህ ቀደም ወደነበረበት 16 ክለቦች ተሳታፊ እንደሚሆኑበት የኢእፌ ገልጿል።

ከጦርነቱ በፊት ፦

➡️ መቐለ 70 እንደርታ ፣

➡️ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ፣

➡️ ስሑል ሽረ ክለቦች በኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ ላይ ተሳታፊ እንደነበሩ ይታወሳል።

በድህረ ገጻችን ኢትዮ አማዞን በመግባት የሚፈልጉትን እቃ ማዘዝ  ብቻ  ሳይሆን የርስዎንም እቃዎች መሸጥ እንደሚችሉ ስናሳውቅዎት በደስታ ነው ። ለማስታወቂያ ወይንም ለመግቢያ ምንም ክፍያ አይጠበቅብዎትም፤  ለተጨማሪ መረጃ   ድህረ ገጻችንን ይጎብኙ። https://ethio-amazon.com/

ለበለጠ መረጃ ሊንኩን በመንካት የቴሌግራም ግሩፓችንን ይቀላቀሉ!https://t.me/ethioamazon

ምንጭ( @tikvahethsport)