እነ ቀሲስ በላይ ክስ እስኪመሰረትባቸው በእስር ይቆያሉ።

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት በነ ቀሲስ በላይ መኮንንና ሌሎች 2 ተጠርጣሪዎች ላይ የክስ መመሥረቻ 15 ቀናት ፈቅዷል።

በሀሰተኛ ሰነድ ከአፍሪካ ኅብረት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ከ6 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ ለማውጣት ሙከራ አድርገዋል ተብለው የተጠረጠሩትና በቁጥጥር ስር የዋሉት ቀሲስ በላይ መኮንንና 2 በወቅቱ አብረዋቸው የነበሩ ግለሰቦች ዛሬ ለ3ኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበው ነበር።

በዚህም ፍርድ ቤት ለዐቃቤ ሕግ 15 ቀናት የክስ መመስረቻ ፈቅዷል።

ተጠርጣሪዎች ክሱ እስኪመሰረት ድረስ ባሉበት ማረፊያ ቤት እንዲቆዩ ፍርድ ቤት አዟል።

በድህረ ገጻችን ኢትዮ አማዞን በመግባት የሚፈልጉትን እቃ ማዘዝ  ብቻ  ሳይሆን የርስዎንም እቃዎች መሸጥ እንደሚችሉ ስናሳውቅዎት በደስታ ነው ። ለማስታወቂያ ወይንም ለመግቢያ ምንም ክፍያ አይጠበቅብዎትም፤  ለተጨማሪ መረጃ   ድህረ ገጻችንን ይጎብኙ። https://ethio-amazon.com/

ለበለጠ መረጃ ሊንኩን በመንካት የቴሌግራም ግሩፓችንን ይቀላቀሉ!https://t.me/ethioamazon

ምንጭ(@tikvahethiopia)