ቲክቶክ ወደ ፍርድ ቤት አመራ።

ቲክቶክ የተሰኘው የቪድዮ ማጋሪያ የማህበራዊ ሚዲያ ለአሜሪካ ኩባንያ የማይሸጥ ከሆነ በመላ አሜሪካ ለመታገድ ተቃርቧል።

እግዱ ተግባራዊ እንዳይደረግ ወይም ውድቅ እንዲሆን ቲክቶክ ወደ አሜሪካ ፍርድ ቤት አምርቷል፤ ሙግትም ከፍቷል።

መተግበሪያው ለፍ/ቤት ባቀረበው የአቤቱታ መዝገብ ” ከ9 ወር – 1 ዓመት ባለው ጊዜ ቲክቶክ ካልተሸጠ #ይታገድ ” የሚለው ሕግ ኢ-ሕገመንግስታዊ ነው ብሎታል።

” ሕጉ የአሜሪካውያንን የመናገር ነጻነትን የሚያደናቅፍ እና ሕጋዊ መረጃን እንዳያገኙ የሚከለክል ነው ” ሲል አክሏል።

አሜሪካ እርምጃውን ለመውሰድ ” ግምታዊ ስጋቶችን ” ብቻ እንዳቀረበች የገለጸው ቲክቶክ ፍርድ ቤት እግዱን እንዲያስቆምለት ጠይቋል።

ባይትዳንስ ኩባንያ ‘ቲክቶክ’ን አሁን ባለው አልጎሪዝም ከመሸጥ አሜሪካ ውስጥ ሙሉ በሙሉ #መዘጋትን እንደሚመርጥ የኩባንያው ምንጮች መናገራቸው ይታወሳል።

አሜሪካም ከሀገር ደህንነት ጋር በተያያዘ ” ካልተሸጠ ይታገድ ” በሚለው ሕግ ላይ አቋሟ ፍጹም የጸና ነው ተብሏል።

በቀሩት ጥቂት ወራት ውስጥ #ካልተሸጠ በመላው አሜሪካ መታገዱ የማይቀርለት ቲክቶክ 170 ሚሊዮን ተጠቃሚዎቹን ያጣል።

በድህረ ገጻችን ኢትዮ አማዞን በመግባት የሚፈልጉትን እቃ ማዘዝ  ብቻ  ሳይሆን የርስዎንም እቃዎች መሸጥ እንደሚችሉ ስናሳውቅዎት በደስታ ነው ። ለማስታወቂያ ወይንም ለመግቢያ ምንም ክፍያ አይጠበቅብዎትም፤  ለተጨማሪ መረጃ   ድህረ ገጻችንን ይጎብኙ። https://ethio-amazon.com/

ለበለጠ መረጃ ሊንኩን በመንካት የቴሌግራም ግሩፓችንን ይቀላቀሉ!https://t.me/ethioamazon

ምንጭ ( @tikvahethiopia )