ቤሊንግሃም ግሪንዉድን ‘ደፋሪ’ ብሎ ተሳድቧል ከተባለ በኋላ ላ ሊጋ ምርመራ ጀመረ

ጌታፌ ከሪያል ማድሪድ በተጫወበት ወቅት የማድሪዱ ጁድ ቤሊንግሃም የጌታፌውን ሜሰን ግሪንውድን “ደፋሪ” ሲል ሰድቦታል ከተባ በኋላ ላ ሊጋው ምርመራ ጀመረ።

ላ ሊጋው ምርመራውን የጀመረው ጌታፌ ተጫዋቹ በማድሪዱ አማካይ “ደፋሪ” ተብሎ ተሰድቧል በሚል ይፋዊ ቅሬታ ለሊጉ ካቀረበ በኋላ ነው።

ላ ሊጋው ምርመራውን የከንፈር እንቅስቃሴን የሚያነቡ ባለሙያዎችን በመቅጠር መጀመሩን ይፋ አድርጓል።

የቀድሞው የማንችስተር ዩናይትድ የክንፍ ተጫዋች ግሪንዉድ የመድፈር ሙከራ እና አካላዊ ጥቃት የሚሉ ክሶች ቀርበውበት ከዩናይትድ ለረዥም ጊዜ ተገልሎ ከቆየ በኋላ ወደ ጌታፌ መዘዋወሩ ይታወሳል።

በክግሪንዉድ ክስ የዐይን ምስክር ተብለው ተመዝግበው የነበሩ ሰዎች እራሳቸውን ከክሱ ማራቃቸውን ተከትሎ እንዲሁም ክሱን የተመለከተ አዲስ ማስረጃ ተገኝቷል በሚል ተጫዋቹ ላይ ቀርበውበት የነበሩት ክሶች በሙሉ ውድቅ ተደርገዋል።

እንደዚያም ቢሆን ግሪንዉድ የቀረቡበት ክሶች ትልቅ ጉዳት አድርሰውበት ከዩናይትድ ካለያየው በኋላ ወደ ስፔን ፊቱን አዙሮ ጌታፌን ተቀላቅሏል።

ከትናንት በስቲያ ሐሙስ በነበረው ጨዋታ በሁለቱ እንግሊዛውያን መካከል አለመግባባቱ የተፈጠረው ቤሊንግሃም ከግሪንዉድ ኳስ ለመንጠቅ ከሞከረ በኋላ ነው። ማድሪድ ከሜዳው ውጪ 2 ለ 0 ባሸነፈበት ጨዋታ ሁለቱ ተጫዋቾች በተለያየ አጋጣሚ ሲጎሻሸሙ ታይተዋል።

ቤሊንግሃም ክስ የቀረበበትን ስድብ ሲሳደብ ይታይበታል የተባለው ተንቀሳቃሽ ምሥል በማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ በስፋት ተሠራጭቷል።

ላ ሊጋው ክስተቱን ተከትሎ ጌታፌ ይፋዊ ቅሬታ ማስገባቱን በገለጸበት መግለጫው “ጌታፌ ለጨዋታ ዳይሬክተር ይፋዊ ቅሬታ አስገብቷል። መደበኛ የአሠራር ሂደትን በመከተል ዳይሬክተሩ ጉዳዩን ለመመርመር እና በጠንካራ ማስረጃ ላይ ተመርኩዞ እርምጃ ለመውሰድ የከንፈር እንቅስቃሴ ንባብ ሪፖርትን ጠይቋል” ብሏል።

ቤሊንግሃም ከጀርመኑ ቦሪሺያ ዶርቱሙንድ ወደ ማድሪድ በ103 ሚሊዮን ፓወንድ ክፍያ ከተዘዋወረ በኋላ በስፔን ጥሩ ጊዜን እያሳለፈ ይገኛል። ቤሊንግሃም በ27 ጨዋታዎች 18 ጎሎችን አስቆጥሯል።

ግሪንዉድ ለአዲሱ ክለቡ ጌታፌ 21 ጊዜ ተሰልፎ 6 ጊዜ ኳስን ከመረብ አገናኝቷል።

በድህረ ገጻችን ኢትዮ አማዞን በመግባት የሚፈልጉትን እቃ ማዝዝ ብቻ ሳይሆን የርስዎንም እቃዎች መሸጥ እንደሚችሉ ስናሳውቅዎት በደስታ ነው ። ለማስታወቂያ ወይንም ለመግቢያ ምንም ክፍያ አይጠበቅብዎትም፤ ለተጨማሪ መረጃ ድህረ ገጻችንን ይጎብኙ። https://ethio-amazon.com/
ለበለጠ መረጃ ሊንኩን በመንካት የቴሌግራም ግሩፓችንን ይቀላቀሉ!https://t.me/ethioamazonnn

ምንጭ ( ቢቢሲ )